Duties and Responsibilities

  1. በህግ ተለይተው በክልሉ መንግሥት እንዲሰበሰቡ የተመደቡትንና ከፌዴራሉ መንግሥት በሚሰጠው ውክልና መሠረት በክልሉ መንግሥት እውቅና የፌዴራሉንና የጋራ ገቢዎችን ይወስናል፣ ይሰበስባል፣
  2. በክልሉ ውስጥ በመካሄድ ላይ ያለውን የታክስ ሥርዓት ማሻሻያ ኘሮግራም አፈጻጸም በባለቤትነት ይመራል፣ ያስተባብራል፣
  3. የታክስ ህጐችን ለማስፈጸም የሚያስፈልጉትንና በማናቸውም ሰው እጅ የሚገኙ ሰነዳችን ይመረምራል፣
  4. ታክስ ከፋዩ ህብረተሰብ ታክስ በፈቃደኝነት የመክፈል ባህልን እንዲያዳብርና መብትና ግዴታውን ጠንቅቆ እንዲረዳ በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨባጫ መድረኮች ትምህርት እንዲሰጥ ያደርጋል፣
  5. የታክስ አስተዳደር ብቃት ያላቸውን ባለሙያዎች ለማፍራት የሚያስችለውን የስልጠናና የሙያ ማሻሻያ ስልቶች ይዘረጋል፣
  6. የታክስ ህጐችን በመጣስ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ይመረምራል፣ ይከሳል፣ ይከራከራል፣ ይህንኑ ለማከናወን የራሱን ዐቃቢያነ-ህግና የታክስ ወንጀል መርማሪዎች ያደራጃል፣ አፈጻጸማቸውን ይቆጣጠራል፣
  7. በክልሉ ውስጥ ዘመናዊ የታክስ አወሳሰንና አሰባሰብ ሥርዓት በመዘርጋት ተግባራዊ ያደርጋል፣ በመስኩ የግልጽነትና የተጠያቂነት መርሆዎችን መሠረት በማድረግ ፍትሐዊ፣ ቀልጣፋና ጥራት ያለው አገልግሎት ይሰጣል፣ ታክስ ነክ መብቶች በአግባቡ እንዲፈጸሙ ያደርጋል፣
  8. በክልሉ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ተመስርቶ የገቢ ጥናቶችን ያካሂዳል
  9. በተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልል ከተሞች ማቋቋሚያ፣ ማደራጃና ሥልጣንና ተግባራት መወሰኛ አዋጅ ቁጥር 91/1996 ዓ.ም. መሠረት ለከተማ አስተዳደሮች የተሰጠው የፊስካል ነጻነት እንደተጠበቀ ሆኖ በከተማ አስተዳደሮች ሥልጣን ሥር የሚሸፈኑ የአገልግሎት ገቢዎችን ይወስናል፣ ይሰበስባል፣ የሙያ ድጋፍ ይሰጣል
  10. ከዚህ በላይ በተራ ቁጥር/10/ የተመለከተው እንደተጠበቀ ሆኖ የከተማ ማዘጋጃ ቤቶችን ገቢ ይወስናል፣ ይሰበስባል፣ የሙያ ድጋፍ ይሰጣል፣
  11. ለታክስ አወሳሰን የሚያስፈልጉትን መረጃዎች ያሰባስባል፣ ያጠናክራል፤ እነዚህኑ በመጠቀም ታክስ ይወስናል፣ ይሰበስባል፣
  12. የታክስ ህጐችን፣ ደንቦችንና መመሪያዎችን ማውጣትና ማሻሻል፣ ሲያስፈልግ ጥናቶችን ያካሂዳል፣ ለክልሉ መንግሥት አቅርቦ ያስወስናል፣
  13. የንብረት ባለቤት ይሆናል፣ ውል ይዋዋላል፣ በስሙ ይከሳል፣ ይከሰሳል፣
  14. ለታክስ ከፋዩ አማራጭ የታክስ መክፈያ ተቋማትን ያመቻቻል፣
  15. የመሥሪያ ቤቱን የአጭር፣የመካከለኛና የረጅም ጊዜ ዕቅድና በጀት አዘጋጅቶ ያቀርባል፣ ሲፈቀድለትም ተግባራዊ ያደርጋል፣ የሥራ እንቅስቃሴዎቹን በሚመለከት ለክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት ወቅታዊ ሪፖርቶችን ያቀርባል፣
  16. የታክስ ወንጀሎችን የመመርመርና የመክሰስ ስልጣኑን እንደአስፈላጊነቱ ለክልሉ ፖሊስ እና የዐቃቢ ህግ አካላት በውክልና ሊሰጥና ሊያሰራ ይችላል፣
  17. ዓላማዎችን ለማስፈጸም የሚረዱ ሌሎች በህግ የተፈቀዱ ተግባራትን ያከናውናል፡፡
  1.  
en_US